Telegram Group & Telegram Channel
Forwarded from Mizan tube (Abdi Ikhlas)
#እንዴት_ታሰርን? – #ኢኽላስ_ጀመዓ

ማክሰኞ እለት ነበር ለመውሊድ ያዘጋጀነውን መንዙማ በቪድዮ ለመሰራት ከጀመዓችን የሴት አባላት የአንዷ አባል እህት ቤት የተገኘነው።

ገና ቀረፃውን ከመጀመራችን ሲቪል እና ዩኒፎርም የለበሱ ፖሊሶች ተከታትለው ገቡ። ግቢ ውስጥ ስለነበር እየቀረፅን የነበረው እንደገቡ አገኙን እኛ እየሰራን የነበረው ሰላማዊ ስራ ስለነበር ቀለል አርገን ተመልክተነው ነበር።

እነሱም ቀለል ባለ ስሜት እያዋዙ ካሜራ እንድናጠፋ ካዘዙን በኋላ ለናንተው ሲባል ነው ፖሊስ ጣብያ ደርሰን ለፎርማሊቲው (ለደንቡ) ሰላማዊ መሆናችሁን ፈርማችሁ ትወጣላችሁ ብለው እኛንም ካሜራ ማኖቻችንንም ይዘውን ሄዱ።

ፖሊስ ጣብያው እንደደረስን እስከ 10 ሰዓት ቁጭ ካረጉን በኋላ ቃል ስጡ አሉን። ቃል ስንሰጥ የተጠረጠርንበት ክስ ይነበብልን ጀመር ያኔ ነው የደነገጥነው እንዴት 1 ሰው ሙስሊም መሆኑ ብቻ አክራሪ ወንጀለኛ ተብሎ ያስከስሰዋል?

ብቻ የሆነው ሆኖ ወደ መምሸት ተቃርቦ 12 ሰዓት ሲሆን ያልጠበቅነው ዱብዳ ወረደ እሱም የጫማ ክር እና ቀበቶ ፍቱ ተባልን ስልካችን ተወሰደና አንዲት ጠባብ ጨለማ ቤት ውስጥ ወረወሩን። በጣም ያስፈራ በጣም ይጨንቅም ነበር ለ 5 ሰው በማይበቃ ቤት ውስጥ አስራ ዘጠኝ ሰው ላይ በላይ አነባበሩን በዛ ላይ ጨለማ። ከዛም አልፎ ለቤተሰቦቻችን ያለንበትን ሁኔታ ለማሳወቅ ስልክ አስደውሉን ብለን ብንለምን ሰሚ ጆሮ ጠፋ።

እዛች ክፍል ውስጥ ታጭቀን አደርን ግማሹ ተኝቶ ግማሹ ቁጭ ብሎ። በዛ ላይ ሽንት ሚሸናው ለሊት 11 ሰዓት እና ማታ 11 ሰዓት 2 ግዜ ብቻ ነው። በድንገት ሰምተው ሊጠይቁን የመጡ ቤተሰቦቻችንም እንዳያዩን ተደረገ።

በቀጣዩ ቀን ልክ 9 ሰዓት አከባቢ ሀይለኛ ዝናብ ላያችን ላይ እየዘነበ በፓትሮል መኪና ጭነውን ቡልቡላ ፖሊስ ጣብያ ወሰዱን።

አልሀምዱሊላህ እዛ ግን ደስ ይል ነበር ቤተሰቦቻችንን ማናገር፣ስልክ መደወል ቻልን ክፍሉም ትልቅ አዳራሽ ነበር ማብራትም አለ ፖሊሶቹም አላህ የወደዳቸው ምርጦች ነበሩ።

ቢሆንም እስር ቤት ነውና በፖሊስ እየተጠበቁ መንቀሳቀስ ከባድ ነው አቀባበላችው ማራኪ ከመሆኑም በላይ ከኛ በፊት ታስረው የነበሩትን 23 አከባቢ እስረኞች ለኛ ቦታውን አስለቅቀው የተሻለ እንክብካቤ ይደረግልን ጀመር። በዛ ላይ ካቦ (የእስረኞች አለቃ) እንደ አዲስ ይመረጥ ተብሎ እኔው ተመረጥኩ 😊

ፖሊሶቹ ለካቦ ቦታ አላቸው በቃ ገብቼ ማላውቀውን እስር ቤት እንደ ለማዳ ታሳሪ ስመራዉ ቆየሁ መሸና ለያንዳንዳችን አንዳንድ ፍራሽ ተሰጥቶን ተመቻችተን አደርን።

በዚህ መሀከል ወደ ደጅ ስንዞር እኛን ለመጠየቅ የመጣው ሰው ወላሂ አጀብ ያሰኛል። ኢኽላስ እውነትም ሰው አለው እንድል አደረገን። ያውም ቁርጡ ሳይታወቅ ለማንም አይነገር ተብሎ እስክንፈታ ድረስ በይፋ ለማንም አልተነገረም ነበር። በአላህ እዝነት በብዙዎች ዱአ በብዙዎች ሩጫና ልፋት መስዋትነት ተከፍሎበት ሀሙስ 9:30 ከእስር ተፈታን።

ውስጥ ባለንበት ሰዓት እንደ ጉድ አሽቀናል ቂሳ እና እስቲግፋር በጋራ ተዋውሰናል ልዩ ትዝታ ልባችን ላይ አትመናል። ክፉና ደጉን ተመልክተናል የቁርጥ ቀን ወዳጃችንንም አይተናል። በዚህ አጋጣሚ ለሊት 12 ሰዓት እየማጣችሁ ቁርስ ምሳ እራት ቡልቡላ ድረስ እያመጣችሁ የእስር ቤቱን ምግብ እንዳንበላ ለካደማችሁን የኢኽላስ ጀመዓ ያልታሰራችሁ ወንድ እና ሴት አባሎቻችን ጓደኞች እና ሌሎች በኛ ጉዳይ የተንከራተታችሁ በሙሉ እኛ አቅም የለንም አላህ ኸይር ጀዛቹን ይክፈል ውዶቼ።

አሁንም የምንለው በዲናችን ምክንያት መታሰር ይብቃን እና ኡስታዛችን ኡስታዝ ፈድሉም እንደኛ ይፈቱልን። እኛ በተፈጠረው ሁሉ ኮራን እንጂ አልተቆጨንም።

ለሌሎች ትምህርት እንሆን ዘንድ ሁላችሁም ራሳችሁን ጠብቁ። አክራሪ አይደለንም እኛ ሙስሊሞች ነን። አልሀምዱሊላህ አላ ኩሊ ሀሊን። 🙏🙏🙏🙏

አብዲ ኢኽላስ

👉 @IkhlassTube



tg-me.com/Ineiyalehucharity/623
Create:
Last Update:

#እንዴት_ታሰርን? – #ኢኽላስ_ጀመዓ

ማክሰኞ እለት ነበር ለመውሊድ ያዘጋጀነውን መንዙማ በቪድዮ ለመሰራት ከጀመዓችን የሴት አባላት የአንዷ አባል እህት ቤት የተገኘነው።

ገና ቀረፃውን ከመጀመራችን ሲቪል እና ዩኒፎርም የለበሱ ፖሊሶች ተከታትለው ገቡ። ግቢ ውስጥ ስለነበር እየቀረፅን የነበረው እንደገቡ አገኙን እኛ እየሰራን የነበረው ሰላማዊ ስራ ስለነበር ቀለል አርገን ተመልክተነው ነበር።

እነሱም ቀለል ባለ ስሜት እያዋዙ ካሜራ እንድናጠፋ ካዘዙን በኋላ ለናንተው ሲባል ነው ፖሊስ ጣብያ ደርሰን ለፎርማሊቲው (ለደንቡ) ሰላማዊ መሆናችሁን ፈርማችሁ ትወጣላችሁ ብለው እኛንም ካሜራ ማኖቻችንንም ይዘውን ሄዱ።

ፖሊስ ጣብያው እንደደረስን እስከ 10 ሰዓት ቁጭ ካረጉን በኋላ ቃል ስጡ አሉን። ቃል ስንሰጥ የተጠረጠርንበት ክስ ይነበብልን ጀመር ያኔ ነው የደነገጥነው እንዴት 1 ሰው ሙስሊም መሆኑ ብቻ አክራሪ ወንጀለኛ ተብሎ ያስከስሰዋል?

ብቻ የሆነው ሆኖ ወደ መምሸት ተቃርቦ 12 ሰዓት ሲሆን ያልጠበቅነው ዱብዳ ወረደ እሱም የጫማ ክር እና ቀበቶ ፍቱ ተባልን ስልካችን ተወሰደና አንዲት ጠባብ ጨለማ ቤት ውስጥ ወረወሩን። በጣም ያስፈራ በጣም ይጨንቅም ነበር ለ 5 ሰው በማይበቃ ቤት ውስጥ አስራ ዘጠኝ ሰው ላይ በላይ አነባበሩን በዛ ላይ ጨለማ። ከዛም አልፎ ለቤተሰቦቻችን ያለንበትን ሁኔታ ለማሳወቅ ስልክ አስደውሉን ብለን ብንለምን ሰሚ ጆሮ ጠፋ።

እዛች ክፍል ውስጥ ታጭቀን አደርን ግማሹ ተኝቶ ግማሹ ቁጭ ብሎ። በዛ ላይ ሽንት ሚሸናው ለሊት 11 ሰዓት እና ማታ 11 ሰዓት 2 ግዜ ብቻ ነው። በድንገት ሰምተው ሊጠይቁን የመጡ ቤተሰቦቻችንም እንዳያዩን ተደረገ።

በቀጣዩ ቀን ልክ 9 ሰዓት አከባቢ ሀይለኛ ዝናብ ላያችን ላይ እየዘነበ በፓትሮል መኪና ጭነውን ቡልቡላ ፖሊስ ጣብያ ወሰዱን።

አልሀምዱሊላህ እዛ ግን ደስ ይል ነበር ቤተሰቦቻችንን ማናገር፣ስልክ መደወል ቻልን ክፍሉም ትልቅ አዳራሽ ነበር ማብራትም አለ ፖሊሶቹም አላህ የወደዳቸው ምርጦች ነበሩ።

ቢሆንም እስር ቤት ነውና በፖሊስ እየተጠበቁ መንቀሳቀስ ከባድ ነው አቀባበላችው ማራኪ ከመሆኑም በላይ ከኛ በፊት ታስረው የነበሩትን 23 አከባቢ እስረኞች ለኛ ቦታውን አስለቅቀው የተሻለ እንክብካቤ ይደረግልን ጀመር። በዛ ላይ ካቦ (የእስረኞች አለቃ) እንደ አዲስ ይመረጥ ተብሎ እኔው ተመረጥኩ 😊

ፖሊሶቹ ለካቦ ቦታ አላቸው በቃ ገብቼ ማላውቀውን እስር ቤት እንደ ለማዳ ታሳሪ ስመራዉ ቆየሁ መሸና ለያንዳንዳችን አንዳንድ ፍራሽ ተሰጥቶን ተመቻችተን አደርን።

በዚህ መሀከል ወደ ደጅ ስንዞር እኛን ለመጠየቅ የመጣው ሰው ወላሂ አጀብ ያሰኛል። ኢኽላስ እውነትም ሰው አለው እንድል አደረገን። ያውም ቁርጡ ሳይታወቅ ለማንም አይነገር ተብሎ እስክንፈታ ድረስ በይፋ ለማንም አልተነገረም ነበር። በአላህ እዝነት በብዙዎች ዱአ በብዙዎች ሩጫና ልፋት መስዋትነት ተከፍሎበት ሀሙስ 9:30 ከእስር ተፈታን።

ውስጥ ባለንበት ሰዓት እንደ ጉድ አሽቀናል ቂሳ እና እስቲግፋር በጋራ ተዋውሰናል ልዩ ትዝታ ልባችን ላይ አትመናል። ክፉና ደጉን ተመልክተናል የቁርጥ ቀን ወዳጃችንንም አይተናል። በዚህ አጋጣሚ ለሊት 12 ሰዓት እየማጣችሁ ቁርስ ምሳ እራት ቡልቡላ ድረስ እያመጣችሁ የእስር ቤቱን ምግብ እንዳንበላ ለካደማችሁን የኢኽላስ ጀመዓ ያልታሰራችሁ ወንድ እና ሴት አባሎቻችን ጓደኞች እና ሌሎች በኛ ጉዳይ የተንከራተታችሁ በሙሉ እኛ አቅም የለንም አላህ ኸይር ጀዛቹን ይክፈል ውዶቼ።

አሁንም የምንለው በዲናችን ምክንያት መታሰር ይብቃን እና ኡስታዛችን ኡስታዝ ፈድሉም እንደኛ ይፈቱልን። እኛ በተፈጠረው ሁሉ ኮራን እንጂ አልተቆጨንም።

ለሌሎች ትምህርት እንሆን ዘንድ ሁላችሁም ራሳችሁን ጠብቁ። አክራሪ አይደለንም እኛ ሙስሊሞች ነን። አልሀምዱሊላህ አላ ኩሊ ሀሊን። 🙏🙏🙏🙏

አብዲ ኢኽላስ

👉 @IkhlassTube

BY እኔ እያለሁ የመረዳጃ ተቋም ( Ineiyalehu )


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/Ineiyalehucharity/623

View MORE
Open in Telegram


እኔ እያለሁ የመረዳጃ ተቋም Ineiyalehu Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram announces Anonymous Admins

The cloud-based messaging platform is also adding Anonymous Group Admins feature. As per Telegram, this feature is being introduced for safer protests. As per the Telegram blog post, users can “Toggle Remain Anonymous in Admin rights to enable Batman mode. The anonymized admin will be hidden in the list of group members, and their messages in the chat will be signed with the group name, similar to channel posts.”

Look for Channels Online

You guessed it – the internet is your friend. A good place to start looking for Telegram channels is Reddit. This is one of the biggest sites on the internet, with millions of communities, including those from Telegram.Then, you can search one of the many dedicated websites for Telegram channel searching. One of them is telegram-group.com. This website has many categories and a really simple user interface. Another great site is telegram channels.me. It has even more channels than the previous one, and an even better user experience.These are just some of the many available websites. You can look them up online if you’re not satisfied with these two. All of these sites list only public channels. If you want to join a private channel, you’ll have to ask one of its members to invite you.

እኔ እያለሁ የመረዳጃ ተቋም Ineiyalehu from tw


Telegram እኔ እያለሁ የመረዳጃ ተቋም ( Ineiyalehu )
FROM USA